Friday, September 1, 2023

"የመሸኛ እና “የእንኳን ደህና መጡ” ፕሮግራም (Farewell and Welcome Program)

 #HMKI ነሐሴ 25 ቀን 2015 ዓ.ም


ነሐሴ 25 ቀን 2015 ዓ.ም የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ብት ልማት ቢሮ እና ማኔጅመንትና ካይዘን ኢንስቲትዩት የማኔጅመንት አባላትና ሠራተኞች “የመሸኛ" ና “የእንኳን ደህና ጡ” ፕሮግራም አካሄዱ። 

ቀደም ሲል የክልሉ መንግስት በክልሉ በየደረጃው በሚገኙ የተለያዩ ዘርፎች የአመራር ሽግሽግ ማድረጉ ይታወሳል።


በዚሁ መሰረት የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ የነበሩ ክብርት ወ/ሮ ፈሪሃ መሀመድን የሴቶች ወጣቶችና ሕጻናት ቢሮ ኃላፊ፣ በተመሳሳይ የሴቶች ወጣቶችና ሕፃናት ቢሮ ኃላፊ የነበሩትን ክብርት ወ/ሮ ደሊላ ዩሱፍ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ሆነው የተሾሙ ሲሆን፣ 

ይህን መሰረት በማድረግ በሁለቱ ተቋማት ሰራተኞችና ማኔጅመንት አባላት በተገኙበት ቀደም ሲል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ነበሩ ክብርት ወ/ሮ #ፈሪሃ_መሀመድ "#የሽኝት" ፕሮግራም እንዲሁም ክብርት ወ/ሮ #ደሊላ_ዩሱፍ "#የእንኳን_ደህና_መጡ" ፕሮግራም በቢሮው እና በኢንስቲትዩቱ ሰራተኞች በደማቅ ስነስርዓት ፕሮግራሙ ተከናውኗል።

No comments:

Post a Comment

የአቅመ ደካማ ቤት ዕድሳት

 HMKI ታህሳስ 4 /2018 ዓም ሥራ አመራርና ከይዘን ኢንስቲትዩት በአሚር ኑር ወረዳ የአቅመ ደካማ ቤት: 300 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ዕድሳቱን አጠናቆ ቤቱን ለወረዳው አስረከበ::