ካይዘን አመራር ፍልስፍና - ሥልጠና
በሥልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሀረሪ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ፈሪሃ መሀመድ እንዳሉት “ከይዘን በክልላችን መተግበር የሚያስገኘውን ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ውስጥ ቀጣይነት ያለው ውጤታማነት፣ ከብክነት የፀዳ ምቹ የስራ ከባቢን በመፍጠር አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ፍልስፍና በመሆኑ፣
ይህን የለውጥ መሳሪያ በተቀናጅና በዕውቀት ተግባራዊ ለማድረግ በተመረጡ የትምህርት ተቋማት ሥልጥናው እንዲሰጥ የተደረገ መሆኑን እና በቀጣይ ሌሎች ተቋማት ላይም መሰል ሥልጠናዎች እንደሚሰጥ፣ በቀጣይ ኢንስቲትዩቱ በክልሉ ከይዘንን ውጤታማ አድርጎ ለማስቀጠል ለተቋማት የሚያደርገውን ድጋፍና ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለፁ ሲሆን፣ በዚህ የሁለት ቀናት የሥልጠና ቆይታችሁ ወቅት ሥልጠናውን በንቃት እንድትከታተሉ” በማለት ሥልጠናው መከፈቱን አብስረዋል። ሥልጠናው ከታህሳስ 21ቀን እስከ ታህሳስ 22/2015ዓ.ም ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ይሆናል።
ወቅታዊና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት:
Blogspot:
https://hmkimedia.blogspot.com/
YouTube ቻነላችን:
https://youtube.com/channel/UCYBkzF7_NRvlk6OvMrNVIrQ
በቴሌግራም:
https://t.me/c/1260317423/383
በፌስቡክ:
https://www.facebook.com/hararimanagement.andkaizeninstitute
በፌስቡክ ገፃችን:
https://www.facebook.com/hararimki
4 Comments
በርቱ ጥሩ ሥራ ነው!
ReplyDeleteእናመሰግናለን
Deletegood job keep it up!
Deletewow good job
ReplyDelete