Skip to main content

Posts

Showing posts from November, 2023

"ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት"

ሀዳር 1 3 ቀን 2016 ዓ.ም #HMKI በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነትና በሶማሌ ክልል አስተናጋጅነት በጅግጅጋ ከተማ የሚከበረው 18 ኛው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓልን አስመልክቶ በ ሀረሪ ህ ዝብ ክ ልል መንግ ስ ት የሥራ አመራርና ከይዘን ኢንስቲትዩት ሠራተኞች ኢፌዴሪ ህገ መንግስትን በተመለከት በተዘጋጀው የጥያቄና መልስ ውድድር ፕሮግራም አካሄዱ። በፕሮግራሙ የተገኙት የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ በርሃኑ ሑንዴ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር በዓሉ ሕዝቦች እኩልነታቸውን፣ አንድነታቸውንና ወንድማማችነታቸውን የሚያጠናክሩበት፥ ባህላዊ እሴቶቻቸውን የሚያንፀባርቁበት፣ ማንነታቸው በሚገባ ያልታወቀላቸው ሕዝቦች እሴቶቻቸውን በአደባባይ የሚያስተዋውቁበት እንደሚሆንም ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በሱማሌ ብሔራዊ ክልል አዘጋጅነት በጅግጅጋ ከተማ የ ሚከበረው የ18ኛው የኢትዮጵ ያ ብሔሮችና ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ን በሚመለከት በክልሉ ለሚገኙ የ መንግስት ተቋማት ሠራተኞች የተዘጋጀ የህገ መንግስት የጥያቄና መል ስ ውድድር በየተቋማቱ በማዘጋጀት የህገ መንግስት ግንዛቤን ለማጎልበት እና በዓሉን ለመታደም ወደ ጅግጅጋ ለሚጓዙ ታዳሚዎች በክልላችን በሚያልፉበት ጊዜ የክልሉ ህዝብ እና የመንግስት ሠራተኛው የዕንግዳ ተቀባይነቱን በተግባር ማሳየት እንዳለበት በመግለፅ ዝግጅቱ መከፈቱን አብስረዋል። በፕሮግራሙ መሰረት በተዘጋጀው የጥያቄና መልስ ውድድር ሦስት የኢንስቲትዩቱ ሠራተኞች የተወዳደሩ ሲሆን፣ የውድድሩ አሸናፊ ለሆኑት ተሳታፊዎች የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።  የዘንድሮው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ከኅዳር 25 እስከ 29 ...

‹‹የስሜት ብልህነት›› Emotional Intelligence

" የስሜት ብልህነት /Emotional Intelligence" #HMKI ጥቅምት 7 ቀን 2016 ዓም የሀረሪ ስራ አመራርና ከይዘን ኢንስቲትዩት ‹‹ የስሜት ብልህነት ›› በሚል ርዕስ ለኢንስቲትዩቱ ፈፃሚዎች ና አመራሮች እንዲሁም ለሴክተር   መ/ቤት ከፍተኛ አመራሮችና ለፈፃሚ ባለሙያዎች ያዘጋጀው ስልጠና በኢንስቲትዩቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተሰጠ ነው።   ስልጠናው በተለያዩ ርዕሶች የሚሰጥ ሲሆን፣ ስለጠናው   ለ 5 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የሆናል። ወቅታዊና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት : በዌብሳይት : Blog https://www.hmkimedia.blogspot.com/ በYoutube  ቻነላችን https://youtube.com/@hmkimedia በቴሌግራም : https://t.me/c/1260317423/383 በፌስቡክ : https://www.facebook.com/hararimanagement.andkaizeninstitute በፌስቡክ ገፃችን: https://www.facebook.com/hararimki በትዊተር፣ https://twitter.com/hararimki?t=j8vGvcUAHxwcw1Sjba3JMA&s=09

የ2016 በጀት፣ የ1ኛው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ

 " የ 2016 በጀት የ 1 ኛው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ " #HMKI ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም በአፈጻጸም ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል እንዲሁም የታዩ ጉድለቶችን ለማረም በሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና የተገኘን እውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት ወደ ተግባር በመቀየር የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም የኢንስቲትዩቱ ሠራተኛ ኃላፊነቱን በመወጣት ጠንክሮ መስራት እንዳለበት ተገለፀ።  መጀመሪያ የኢንስቲትዩቱን የ 2016 በጀት ዓመት መደበኛ ዕቅድ የ 1 ኛው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ከኢንስቲትዩቱ ሠራተኞች ጋር በመሆን የገመገመ ሲሆን፣ በአፈፃፀም ሂደት የታዩ ጉድለቶችን እንዲሁም ያጋጠሙ ችግሮችን፣ በመገምገም በቀጣይ ሊስተካከሉ የሚገባቸውን በመለየት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል እንዲሁም የታዩ ጉድለቶችን በማረም የተሻለ የአፈጻጸም ውጤት ለማምጣት ሁሉም ሰራተኛ ተቀናጅቶ በቡድን ስሜት መስራት እንዳለበት መግባባት ላይ ተደርሷል። በመጨረሻም ጥቅምት 28/2016 የቡድን ሥራ (Team Building) በስልጠናው የተገኘውን እውቀት፣ ክህሎትና ባህሪን በማቀናጀት በቀጣይ በቡድን ሥራ በመመራት የተሻለ የአፈፃፀም ለማስመዝገብ መላው የተቋሙ ሠራተኛ መስራት እንደሚገባ እና በአፈፃፀም ሂደት የታዩ ጠንካራ አፈፃፀምን በማስቀጠል እና ደካማ ጎኖች ለማረም የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ፣ ጥቅምት 27-28 ቀን 2016 ዓም ለሁለት ቀን ሲካሄድ የነበረው የአፈፃፀም ግምገማና ሲሰጥ የነበረው አቅም ግንባታ ሥልጠና ተጠናቀቀ።